በ አድሀቂግቢ የምርጫ ስነ ስርአት
በ
ቤዛዊት
ተፈሪ(መቀሌ
ዩንቨርስቲ)
ግንቦት 16 ቀን 2007 ዐ.ም በአድ ሃቂ ካምፓስ የሚገኙ ተማሪዎች ሀገር አቀፉን ምርጫ ሲመርጡ ውለዋል ።
የግቢው ምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴም ከምርጫው አንድ ቀን ቀደም ብሎ ጀምሮ እስከ ምርጫው ማግስት ድረስ ተማሪውን ሲያዝናና እንዲሁም ለምርጫ ሲያነሳሳ ቆይቷል ።
በምርጫው ቀንም ብዙ ተማሪዎች የፈለጉትን ፓርቲ በነፃነት ሲመርጡ ውለዋል ። ወረቀት አልመጣም ነገ መታቹ ምረጡ የተባሉ ተማሪዎችም ሲያማርሩ ውለዋል ።
ምርጫው በ ኤፍ ና ኬ ህንፃዎች ውስጥ የተካሄደ ሲሆን ህንፃውን በዞንና በክልል በመከፋፈል ለተማሪዎች ቀልጣፋና ምቹ የአመራረጥ ሂደት እንዲፈጠር ተደርጓል ።
በምርጫ ማግስትም ግቢያችን ሌላ ምርማ አስተናግዶ ውሏል ።ከተለያዩ አካባቢዎች ወረቀት ባለመድረሱ ምክንያት ለምሳሌ ተምቤን አድዋ አካባቢ የመጡ ለጆች በምርጫም ማግስት ድምፃቸውን ለመስጠት በቅተዋል ።
ባጠቃላይ በግቢያችን ሰላማዊ ምርጫ ሲካሄድ ውሏል።
No comments:
Post a Comment